Home የማዕከሉ የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት በፍላጎት ላይ የተመሠረተ የዳሰሳ ጥናት በማድረግ በፀረ ሙስና ህጎቸ፣ አዋጆችና መመሪያዎች እንዲሁም ግብረ ገብነትን ያማከለ ስልጠና ሰጠ፡፡

የማዕከሉ የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት በፍላጎት ላይ የተመሠረተ የዳሰሳ ጥናት በማድረግ በፀረ ሙስና ህጎቸ፣ አዋጆችና መመሪያዎች እንዲሁም ግብረ ገብነትን ያማከለ ስልጠና ሰጠ፡፡

16th November, 2025

ኅዳር 2/2018 ዓ.ም

በምርታማነት ማሻሻያ የልህቀት ማዕከል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት በፍላጎት ላይ የተመሠረተ የዳሰሳ ጥናት በማድረግ በፀረ ሙስና ህጎቸ፣ አዋጆችና መመሪያዎች እንዲሁም ግብረ ግብረ ገብነት ላይ ያተኮረ ስልጠና ለማዕከሉ ሰራተኞች የሰጠ ሲሆን በስልጠናው ላይ ከሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በመጡ ባለሙያ ስልጠናው ተሰጥቷል፡፡

በዚህም በስልጠናው ላይ የተለያዩ ርዕሶች የተነሱ ሲሆኑ ከነዚህም መካከል፡- የምግባር ምንነት፣ ግብረገባዊ ግዴታዎች፣ የግብረ ገብ እሴት ማዳበር ዓላማው፣ እንዲሁም የአመራርና የሰራተኞች ግብረ ገብ ምን መምሰል አለበት በሚሉ ዙያዎች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቶበታል፡፡ 

ምርታማነት ማሻሻያ የልህቀት ማዕከል

.

Copyright © All rights reserved.

Created with